Thursday, January 10, 2013

ምልማድ


የሚከተሉትን መራሕያን ከግሶች ጋር አዛምድ /አስተፃምር/
፩. አንትን ሀ. ነበርኩ ረ. መጽአት
፪. ውእቱ ለ. በላዕነ ሰ. ኖምክሙ
፫. አነ ሐ. ሖርኪ ሸ. ሖራ
፬. ውእቶን መ. ጸለዩ ቀ. በልዐ
፭. ይእቲ ሠ. ቀተልክን
አስተካክለህ ጻፍ / በስርዓተ- ሰዋስው/
ምሳሌ: /ኀዘነ/ ማርያም አመ /ተሰቅለ/ ክርስቶስ => ኀዘነት

 ማርያም አመ ተሰቅለ ክርስቶስ።
፩. /ኖመ/ አንተ ላዕለ አራት /አልጋ/
፪. /ሖረ/ አንትን ኀበ ደብረ ጽጌ
፫. /ቆመ/ ማርታ ወማርያም ቅድመ ቤተ መቅደስ
፬. /ኀደረ/ ፍሬ ጽድቅ ውስተ ቤተ አርድዕት /ተማሪዎች/
፭. /አርመመ/ ሚካኤል አመ ተሰቅለ አምላኩ
፮. /ተፈስሐ/ ጻድቃን በእግዚአብሔር
ወልጥ ኀበ ልሳነ ዐምሐራ /ወደ አማርኛ መልስ/
፩. ንሕነ ሖርነ ኀበ አክሱም ወላስታ
፪. አንቲ ውእቱ እመ ብርሃን
፫. ማርያም ወለደት ወልዳ ዘበኩራ
፬. አንተ ወአነ ሰማዕነ ቃለ እግዚአብሔር
፭. እለመኑ /እነማን/ ውእቶሙ ዘሖሩ ኀበ ገዳመ ሲና
ወደ ግእዝ መልስ /ወልጥ ኀበ ልሳነ ግእዝ/
፩. ወደ ጸሎት ቤት ሄድን።
፪. እኔ ነኝ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሄድኩ። /ዘ = የ/
፫. እነርሱ በኅብረት ተቀመጡ። /ኅቡረ = በኅብረት/
፬. ቶማስ እና ጴጥሮስ መምህራን ናቸው።
፭. ማርያም ድንግል የአሮን በትር /በትር = በትር/ ናት።
፮. አንተ የክርስቶስን ወንጌል ሰበክህ።
፯. አንተ ሰባኪ አይደለኽም።
፪.፩.፫. መራሕያን እንደ አመልካች ቅጽል
የመራሕያን ሌላው አገልግሎታቸው አንድን ነገር ወይም አካል በተባዕትና በአንስት፣ በማይታይና በሚታይ፣ በቅርብ ሩቅና በቅርብ ቅርብ አመልካች ጠቋሚ እየኾኑ መነገራቸው ነው። በሊቃዉንት መጻሕፍት ጉልት እየተባሉ ይጠቀሳሉ።
መደባቸዉም ሦስት ሲሆኑ እነዚኽም፦
፩. ተናጋሪን /እኔን ባይ/ አመልካቾች
፪. የማይታይ አመልካቾች
፫. የሚታይ አመልካቾች ናቸው። በተጨማሪ የቅርብ ሩቅ አመልካች ሆነው ሲገለጹ ደግሞ፦
ውእቱ ዝኩ ተብሎ ይገለጻል። ትርጉሙም ያ
ይእቲ እንትኩ >> >> ያቺ
ውእቶሙ እልኩ >> >> እኒያ /እነዚያ/
ውእቶን እልኮን >> >> እኒያ /ለሴቶች/
የሚከተሉትን ቃላት በማጥናት ከላይ ባየናቸው የመራሕያን አገልግሎት የራሳችሁን መልመጃዎች ሥሩ።
ሀ. ቃላት
ከመ = እንደ ወ = እና ጥቀ = እጅግ
አይቴ = ወዴት ማዕዜ = መቼ ናሁ = አሁን ፣ እነሆ
ምስለ = ጋር ምንት = ምን
እም = ከ በእንተ = ስለ
አላ = እንጂ ዝየ = እዚህ
ህየ = እዚያ ዮም = ዛሬ
ጌሠም = ነገ ትማልም = ትላንት
ዘ = እንተ = የ እለ ፣ ዘ = የ /ለብዙ/
(ዘሖረ = እንተ ሖረ =የሄደ) ምሳሌ: እለ ሖሩ = ዘሖሩ = የሄዱ
የቤተሰብእ ስም
ነጠላ ብዙ
አብ = አባት አበው = አባቶች
እም = እናት እማት = እናቶች
ወልድ = ልጅ /ወንድ/ ውሉድ = ልጆች
ወለት = ሴት ልጅ አዋልድ = ሴት ልጆች
እኅት = እኅት አኀት = እኅቶች
እኁ = ወንድም አኀው = ወንድሞች
አመት = ሴት አገልጋይ አእማት = ሴት አገልጋዮች
ገብር = ወንድ አገልጋይ አግብርት = ወንድ አገልጋዮች
ለ. የግስ ቃላት
ሖረ = ሄደ ፤ ቆመ = ቆመ ፤ ኖመ ፣ ደቀሰ = ተኛ
ጸለየ = ልመና አቀረበ ፤ ሰአለ = ለመነ ፣ ጠየቀ ፤ ነበረ = ተቀመጠ ፤ ኀደረ = አደረ
አርመመ = ዝም አለ ፤ ተፈስሐ = ተደሰተ ፤ ሰብሐ = አመሰገነ
በልዐ = በላ ፤ መጽአ = መጣ ፤ ቀተለ = ገደለ ሰትየ = ጠጣ
ምልማድ /መልመጃ/
የ “ሀ” ን ቃላት ከ “ለ” ቃላት ጋር /መራሕያኑን ከግሶች/ አዛምድ /አስተፃምር ቃላተ “ሀ” ምስለ ቃላተ “ለ”/
“ሀ” “ለ”
፩. አንትን አ. ነበርኩ
፪. ውእቱ በ. በላዕነ
፫. አነ ገ. ሖርኪ
፬. ውእቶን ደ. ቀተልክን
፭. ይእቲ ሀ. መጽአት
፮. ንሕነ ወ. ኖምክሙ
፯. አንቲ ዘ. ሖራ
፰. ውእቶሙ ሐ. በልዐ
፱. አንትሙ ጠ. ጸለዩ
ወልጥ ኀበ ልሳነ ዐምሐራ /ወደ አማርኛ ለውጥ/
፩. ንሕነ አብደርነ /አብደረ = መረጠ/ ንትገደፍ /ገደፈ = ተወ ፣ ጣለ/ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር እም ንንበር ውስተ ቤተ ኃጥአን።
፪. አንቲ ውእቱ መሶበ ወርቅ ንጹሕ
፫. አንተ ወአነ ሖርነ ኀበ መካነ ምስያጥ /ገበያ/
፬. ወለተ ማርያም ነጸረት መንገለ /ወደ/ ምስራቅ
፭. አንትሙ ሖርክሙ ኀበ ኢየሩሳሌም
፮. እለመኑ ውእቶሙ ዘነገዱ ኀበ ብሔረ እስራኤል
፯. ንሕነ ጸለይነ በእንተ ዴር ሡልጣን
፰. ውእቶሙ ተዐቀቡ እም ኤድስ
፱. አንትሙ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር
፲. አነ ደቀስኩ ላዕለ አራትየ
ወልጥ ኀበ ልሳነ ግእዝ
፩. አንተ አውሮጳዊ አይደለህም።
፪. የእናትህ ስሟ ማነው?
፫. ወንድሞች ወደ ቤተ ክርስቲያን መጡ።
፬. ሰሎሞን ወደ አባቶች ሄደ።
፭. ዝም ብሎ ተቀመጠ።
ትውውቅ /ሰላምታ/
ዜና ሥላሴ ቤዛ ማርያም
ሰላም ለከ እኁየ ወሰላም ለከ እኁየ
ሰላም ላንተ ይሁን ወንድሜ ሰላም ላንተም ይሁን
እፎ ሐሎከ እግዚአብሔር ይሰባሕ
እንዴት አለህ? እግዚአብሔር ይመስገን
መኑ ስምከ ቤዛ ማርያም ውእቱ ስምየ
ስምህ ማነው? ስሜ ቤዛ ማርያም ነው
ወመኑ ስመ አቡከ ዘድንግል ውእቱ ስመ አቡየ
የአባትህስ ስም ማነው? የአባቴ ስም ዘድንግል ነው
ወመኑ ስመ እምከ አስካለ ማርያም ውእቱ ስመ እምየ
እም አይቴ መጻእከ እም ጎጃም
ከየት ነው የመጣህ? ከጎጃም
እስፍንቱ አዝማኒከ ዕሥራ ወአሐዱ
ዕድሜህ ስንት ነው? ሃያ አንድ
ናሁ…ኀበ አይቴ ውእቱ ዘተሐውር ኀበ ከኒሳ
አሁን ወደ የት ነው የምትሄደው? ወደ ቤተ ክርስቲያን
እም አይቴ ውእቱ ዘትመጽእ ናሁ
እም መካነ ምሥያጥ አኹን ከየት ነው የምትመጣው?
ከገበያ ኦሆ = እሽ
ሰናይ ምስየት ለኲልነ
መልካም ምሽት ለኹላችን

ግእዝ ክፍል ሁለት : ሰዋስወ ግእዝ


ሰዋስወ ግእዝ

፪.፩. መራሕያን
መርሐ /መራ/ ከሚለው ግስ የተገኘ ሲሆን መሪዎች ፊታውራሪዎች የሚለውን ትርጉም ይይዛል። መራሕያን የሚባሉት በግእዝ ልሣን አስር ናቸው።
እነሱም ፦
አነ ………………………………እኔ
አንተ ……………………………አንተ
አንቲ ……………………………አንቺ
ውእቱ ……………………………እሱ
ይእቲ …………………………….እሷ
ንሕነ ……………………………..እኛ
አንትሙ ………………………….እናንተ /ለቅርብ ወንዶች/
አንትን ……………………………እናነተ /ለቅርብ ሴቶች/
ውእቶሙ /እሙንቱ/ …………….እነርሱ /ለሩቅ ወንዶች/
ውእቶን /እማንቱ/ …………………እነርሱ /ለሩቅ ሴቶች/
የመራሕያን አገልግሎት ሦስት ዓይነት ነው፡፡ ይኸዉም ፦
፩.፩. ተውላጠ ስም በመሆን
፩.፪. የመሆን ግስ /ነባር አንቀጽ/ በመሆንና
፩.፫. አመልካች ቅጽል በመሆን
፪.፩.፩. መራሕያን ምድብ ተውላጠ - ስሞች / pronouns /

መደብ ጾታ ነጠላ ቁጥር ብዙ ቁጥር
ሣልሳይ /ሦስተኛ መደብ/ ተባዕታይ ውእቱ ውእቶሙ /እሙንቱ/
አንስታይ ይእቲ ውእቶን /እማንቱ/
ካልኣይ /ኹለተኛ መደብ/ ተባዕታይ አንተ አንትሙ
አንስታይ አንቲ አንትን
ቀዳማይ /፩ኛ መደብ/ የወል አነ ንሕነ

በስም ፋንታ ተተክቶ የሚያገለግል ቃል ተውላጠ-ስም ይባላል። መራሕያን እንደ ተውላጠ-ስም ሲሆኑ በስም ፋንታ ተተክተው የሚነገሩ የርባታ መደቦች ናቸው። እነሱም የአካል፣ የስምና የስም አጸፋ እየሆኑ በወንድና በሴት፣ በሩቅና በቅርብ፣ በነጠላና በብዙ የሚነገረውን ርባታ ያሳያሉ። አስሩም መራሕያን በነጠላና በብዙ፣ በወንድና በሴት፣ በሩቅና በቅርብ ሲከፈሉ ሦስት መደብ ይሆናሉ።
ይኸዉም፦
፩. ቀዳማይ መደብ / 1st person/ አንደኛ መደብ፡ የወል ጾታ
አነ => እኔ = I
ንሕነ => እኛ = we
፪. ካልኣይ መደብ /2nd person/ ኹለተኛ መደብ፡
አንተ => በቁሙ = you
አንቲ => አንተ = you
አንትሙ => እናንተ = you (ለቅርብ ወንዶች)
አንትን => እናንተ = you (ለቅርብ ሴቶች)
፫. ሣልሳይ መደብ / 3rd person / ሦስተኛ መደብ፡
ውእቱ => እሱ = He
ይእቲ => እሷ = She
ውእቶሙ => እነሱ (እነዚያ) = They (ለሩቅ ወንዶች)
ውእቶን => እነሱ (እነዚያ) = They (ለሩቅ ሴቶች)
፩.፩. መራሕያን ምድብ ተውላጠ-ስሞች በዐረፍተ- ነገር
ተውላጠ-ስሞች ቀደሰ፣ ሖረ እና ሰገደ በሚሉት ቀዳማይ አንቀጾች ዐረፍተ- ነገር ሲመሠርቱ፦
ሀ. ቀደሰ / ቀዳማይ አንቀጽ፡ past tense/
አነ ቀደስኩ - እኔ አመሰገንሁ
አንተ ቀደስከ - አንተ አመሰገንህ
አንቲ ቀደስኪ - አንቺ አመሰገንሽ
ውእቱ ቀደሰ - እሱ አመሰገነ
ይእቲ ቀደሰት - እሷ አመሰገነች
ንሕነ ቀደስነ - እኛ አመሰገን
አንትሙ ቀደስክሙ - እናንተ አመሰገናችሁ
አንትን ቀደስክን - እናንተ አመሰገናችሁ (ለሴቶች)
ውእቶሙ ቀደሱ - እነሱ አመሰገኑ
ውእቶን ቀደሳ - እነሱ አመሰገኑ (ለሴቶች)
ማስታወሻ
• ውእቱ / ቀደሰ/ እና ይእቲ /ቀደሰት/ ከሚሉት ውጭ በሌሎች መራሕያን "ሰ" የሚለው ፊደል ወደ ሳድስ፣ ራብዕና ሳብዕ ይለወጣል፡፡
ለ. ሖረ = ሄደ /went/ ፣ ኀበ = ወደ
አነ ሖርኩ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - እኔ ወደ እግዚአብሔር ቤት ኼድኩ።
አንተ ሖርከ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - አንተ ወደ እግዚአብሔር ቤት ኼድክ።
አንቲ ሖርኪ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - You went to church (house of God).
ውእቱ ሖረ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - He went to church.
ይእቲ ሖረት ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ንሕነ ሖርነ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
አንትሙ ሖርክሙ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
አንትን ሖርክን ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ውእቶሙ ሖሩ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ውእቶን ሖራ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ሐ. ሰገደ = ሰገደ ፣ቅድመ = ፊት ለፊት
አነ ሰገድኩ ቅድመ ቤተ መቅደስ - በቤተ መቅደስ ፊት ሰገድሁ ።
አንተ ሰገድከ ቅድመ ቤተ መቅደስ - You fell on in front of church.
አንቲ ሰገድኪ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቱ ሰገደ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ይእቲ ሰገደት ቅድመ ቤተ መቅደስ
ንሕነ ሰገድነ ቅድመ ቤተ መቅደስ
አንትሙ ሰገድክሙ ቅድመ ቤተ መቅደስ
አንትን ሰገድክን ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቶሙ ሰገዱ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቶን ሰገዳ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ማስታወሻ
የግሱ መጨረሻ ፊደል ‹ከ› ፣‹ቀ› ፣‹ገ› ን የመሰለ ከሆነ ከዚያው ላይ ፊደሉን በማጥበቅ (አነ ፣አንተ ፣አንቲ፣ አንትሙ፣ አንትን ሲሆኑ) ይነበባል። ምሳሌ ሰበከ ብሎ አነ ሰበኩ ይባላል (ኩ ጠብቃ ትነበባለች) እንጅ አነ ሰበክኩ አይባልም። አነ አጥመቁ ይላል እንጅ አነ አጥመቅኩ አይልም። ስለሆነም ማጥበቅ አለብን።
፪.፩.፪. መራሕያን እንደ ነባር አንቀጽ / verb to be/
ነባር አንቀጽ ሲባል ማሰሪያ ግስ ማለት ነው። መራሕያን በአንቀጽነታቸው እየተተረጎሙ ሲፈቱ ማሠሪያ ይሆናሉ። ይኸዉም፦
ውእቱ = ነው፣ ኾነ፣ ነበረ፣ ኖረ፣ ይኑር፣ ነሽ፣ ነኝ፣ ነኽ፣ ናችሁ፣ ነበራችሁ
ይእቲ = ናት፣ ነበረች
ውእቶሙ(እሙንቱ) = ናቸው፣ ሆኑ፣ ነበሩ፣ ኖሩ፣ ይኑሩ ( ለወንዶች)
ውእቶን(እማንቱ) = ናቸው፣ ነበሩ (ለሴቶች)
አንተ = ነህ፣ ሆንክ፣ ነበርክ፣ ኖርክ፣ ኑር
አንቲ = ነሽ፣ ኾንሽ፣ ነበርሽ፣ ኖርሽ፣ ኑሪ
አንትሙ(ተባዕት) = ናችኹ፣ ኾናችኹ፣ ነበራችኹ፣ ኖራችኹ፣ ኑሩ
አንትን(አንስት) = ናችኹ፣ ኾናችኹ፣ ነበራችኹ፣ ኖራችኹ፣ ኑሩ
ንሕነ = ነን፣ ኾንን፣ ነበርን፣ ኖርን፣ እንኑር
አነ = ነኝ፣ ኾንኩ፣ ነበርኩ፣ ኖርኩ፣ ልኑር
ምሳሌ፦
አነ ውእቱ ጒንደ ወይን = እኔ የወይን ግንድ ነኝ።
አነ ውእቱ ኖላዊ ኄር = እኔ ቸር ጠባቂ ነኝ።
አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም= የአዳም /ለአዳም/ ተስፋው አንቺ ነሽ።
አንተ ውእቱ ዕጣን ኦ መድኃኒነ = መድኃኒታችን ሆይ አንተ ዕጣን ነህ።
ማርያም ይእቲ መሠረተ ሕይወት = ማርያም የሕይወታችን መሠረት ናት።
ናሆም ወሚልክያስ ነቢያት ውእቶሙ /እሙንቱ/ = ናሆምና ሚልክያስ ነቢያት ናቸው።
አስቴር ወሶስና ቅዱሳን ውእቶን /እማንቱ/ = አስቴርና ሶስና ቅዱሳን ናቸው።
ውእቱ ለዋጭ ተለዋጭ ባሕርይ ስላለው በተባዕትና በአንስት በብዙና በነጠላ አፈታት ይፈታል። እንዲህ ማለት በነባር አንቀጽነቱ የሚከተሉትን ትርጉም ሊያስገኝ ይችላል። በዐረፍተ- ነገር እየገባ ሲታይ የትኛውን ትርጉም እንደያዘ ዐመሉን ማስተዋል ያስፈልጋል።
ውእቱ = ነው፣ ናት፣ ናቸው /ተ/አ/፤
= ነኽ፣ ነሽ፣ ናችኹ /ተ/አ/ ፤
= ነኝ፣ ነን፣ ይኾናል
ሥርዓተ ዐረፍተ- ነገር በምሳሌ፦
• ቅድስት ይእቲ ኤልሳቤጥ = ኤልሳቤጥ ቅድስት ናት
• ኤልሳቤጥ ቅድስት ይእቲ
• ነቢይ ውእቱ ሕዝቅኤል
• ሕዝቅኤል ነቢይ ውእቱ
ውእቱ ለሚለው አሉታው አኮ /አይደለም/ ነው
ለምሳሌ፦ አኮ ነቢይ ሕዝቅኤል
ተጨማሪ ምሳሌዎች:
አነ ውእቱ ፍኖተ ጽድቅ = እኔ የእውነት መንገድ ነኝ
አንተ ውእቱ ቤዛ ኵሉ ዓለም = አንተ የዓለም ሁሉ ቤዛ ነህ
ጳዉሎስ ወጴጥሮስ መምህራን ውእቶሙ
ሰሎሜ ወኤልሳቤጥ ቅዱሳት ውእቶን

አበዊነ መሀሩነ ልሳነክሙ ወቃለ እግዚአብሔር

ግእዝ ክፍል አንድ : የግእዝ ፊደላትና ትርጉማቸው

የግእዝ ፊደላትና ትርጉማቸው

ፊደል ስመ ትርጓሜሁ የስማቸው ትርጓሜ 
‹‹ሀ››...ብሂል…..........ሀልዎቱ ለአብ…........የአብ አኗኗሩ
‹‹ለ››. .ለብሰ ሥጋነ ወፆረ ሕማመነ...የእኛን ሥጋ ለብሶ ሕማማችንን ተሸከመ
 ‹‹ሐ››.........ሕያው እግዚአብሔር…..እግዚአብሔር ዘለዓለማዊ ነው 
‹‹መ››…...............መጽአ ውስተ ዓለም...........ወደ ዓለም መጣ
‹‹ሠ››.......ሠረቀ እም ድንግል በሥጋ.........ከድንግል በሥጋ ተወለደ 
‹‹ረ››............ረግዐ ሰማይ ወምድር..............…ሰማይና ምድር ፀና
‹‹ሰ››…..........ሰፋኒ እግዚአብሔር......እግዚአብሔር ምሉዕ ነው 
‹‹ቀ››…...............ቀዳሚሁ ቃል…................መጀመሪያ ቃል ነበር
‹‹በ››…......ባዕል እግዚአብሔር........…እግዚአብሔር ባዕለ ፀጋ ነው 
‹‹ተ››…................ተሰብአ ወተሠገወ...........................…ፍጹም ሰው ሆነ
‹‹ኀ››...................ኃያል እግዚአብሔር….....................እግዚአብሔር ኃያል ነው
 ‹‹ነ››...ነሥአ ሥጋ እም ቅድስት ድንግል...ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋን ነሳ 
‹‹አ››...................አብ አሐዜ ኵሉ..........................…ዓለምን የያዘ አብ ነው
‹‹ከ››..................ከሃሊ እግዚአብሔር........................…እግዚአብሔር ቻይ ነው 
‹‹ወ››....ወረደ ወተሠገወ.…ከሰማየ ሰማያት ወረደ ሰውም ሆነ
‹‹ዐ››..................ዐቢይ እግዚአብሔር.....................…እግዚአብሔር ታላቅ ነው
‹‹ዘ››..................ዘምሩ ለእግዚአብሔር.................…እግዚአብሔርን አመስግኑ 
‹‹የ››…..የማነ እግዚአብሔር........የእግዚአዘብሔር እጅ ድንቅ ነገር አደረገች 
‹‹ደ››........ደመረ ሥጋነ ምስለ መለኮቱ...…ሥጋችንን ከመለኮቱ ጋር አዋሐደ 
‹‹ገ››….............ገብረ ሰማየ ወምድረ....................….ሰማይንና ምድርን ፈጠረ 
‹‹ጠ››…ጣዕሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር...እግዚአብሔር ቸር መሆኑን አውቃችሁ ቅመሱ
‹‹ጰ››…........ጰራቅሊጦስ…..............መንፈስ ቅዱስ
‹‹ጸ››…...........ፀሐየ ጽድቅ እግዚአብሔር…..... እግዚአብሔር እውነትኛ ፀሐይ ነው
 ‹‹ፈ››…..........ፈጠረ ሰማየ ወምድረ…....................ሰማይንናምድርን ፈጠረ
‹‹ፐ››…........ፓፓኤል እግዚአብሔር…...................ፋኖስ መንፈስ