Thursday, January 10, 2013

ግእዝ ክፍል አንድ : የግእዝ ፊደላትና ትርጉማቸው

የግእዝ ፊደላትና ትርጉማቸው

ፊደል ስመ ትርጓሜሁ የስማቸው ትርጓሜ 
‹‹ሀ››...ብሂል…..........ሀልዎቱ ለአብ…........የአብ አኗኗሩ
‹‹ለ››. .ለብሰ ሥጋነ ወፆረ ሕማመነ...የእኛን ሥጋ ለብሶ ሕማማችንን ተሸከመ
 ‹‹ሐ››.........ሕያው እግዚአብሔር…..እግዚአብሔር ዘለዓለማዊ ነው 
‹‹መ››…...............መጽአ ውስተ ዓለም...........ወደ ዓለም መጣ
‹‹ሠ››.......ሠረቀ እም ድንግል በሥጋ.........ከድንግል በሥጋ ተወለደ 
‹‹ረ››............ረግዐ ሰማይ ወምድር..............…ሰማይና ምድር ፀና
‹‹ሰ››…..........ሰፋኒ እግዚአብሔር......እግዚአብሔር ምሉዕ ነው 
‹‹ቀ››…...............ቀዳሚሁ ቃል…................መጀመሪያ ቃል ነበር
‹‹በ››…......ባዕል እግዚአብሔር........…እግዚአብሔር ባዕለ ፀጋ ነው 
‹‹ተ››…................ተሰብአ ወተሠገወ...........................…ፍጹም ሰው ሆነ
‹‹ኀ››...................ኃያል እግዚአብሔር….....................እግዚአብሔር ኃያል ነው
 ‹‹ነ››...ነሥአ ሥጋ እም ቅድስት ድንግል...ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋን ነሳ 
‹‹አ››...................አብ አሐዜ ኵሉ..........................…ዓለምን የያዘ አብ ነው
‹‹ከ››..................ከሃሊ እግዚአብሔር........................…እግዚአብሔር ቻይ ነው 
‹‹ወ››....ወረደ ወተሠገወ.…ከሰማየ ሰማያት ወረደ ሰውም ሆነ
‹‹ዐ››..................ዐቢይ እግዚአብሔር.....................…እግዚአብሔር ታላቅ ነው
‹‹ዘ››..................ዘምሩ ለእግዚአብሔር.................…እግዚአብሔርን አመስግኑ 
‹‹የ››…..የማነ እግዚአብሔር........የእግዚአዘብሔር እጅ ድንቅ ነገር አደረገች 
‹‹ደ››........ደመረ ሥጋነ ምስለ መለኮቱ...…ሥጋችንን ከመለኮቱ ጋር አዋሐደ 
‹‹ገ››….............ገብረ ሰማየ ወምድረ....................….ሰማይንና ምድርን ፈጠረ 
‹‹ጠ››…ጣዕሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር...እግዚአብሔር ቸር መሆኑን አውቃችሁ ቅመሱ
‹‹ጰ››…........ጰራቅሊጦስ…..............መንፈስ ቅዱስ
‹‹ጸ››…...........ፀሐየ ጽድቅ እግዚአብሔር…..... እግዚአብሔር እውነትኛ ፀሐይ ነው
 ‹‹ፈ››…..........ፈጠረ ሰማየ ወምድረ…....................ሰማይንናምድርን ፈጠረ
‹‹ፐ››…........ፓፓኤል እግዚአብሔር…...................ፋኖስ መንፈስ

No comments:

Post a Comment