የሚከተሉትን መራሕያን ከግሶች ጋር አዛምድ /አስተፃምር/
፩. አንትን ሀ. ነበርኩ ረ. መጽአት
፪. ውእቱ ለ. በላዕነ ሰ. ኖምክሙ
፫. አነ ሐ. ሖርኪ ሸ. ሖራ
፬. ውእቶን መ. ጸለዩ ቀ. በልዐ
፭. ይእቲ ሠ. ቀተልክን
አስተካክለህ ጻፍ / በስርዓተ- ሰዋስው/
ምሳሌ: /ኀዘነ/ ማርያም አመ /ተሰቅለ/ ክርስቶስ => ኀዘነት
ማርያም አመ ተሰቅለ ክርስቶስ።
፩. /ኖመ/ አንተ ላዕለ አራት /አልጋ/
፪. /ሖረ/ አንትን ኀበ ደብረ ጽጌ
፫. /ቆመ/ ማርታ ወማርያም ቅድመ ቤተ መቅደስ
፬. /ኀደረ/ ፍሬ ጽድቅ ውስተ ቤተ አርድዕት /ተማሪዎች/
፭. /አርመመ/ ሚካኤል አመ ተሰቅለ አምላኩ
፮. /ተፈስሐ/ ጻድቃን በእግዚአብሔር
ወልጥ ኀበ ልሳነ ዐምሐራ /ወደ አማርኛ መልስ/
፩. ንሕነ ሖርነ ኀበ አክሱም ወላስታ
፪. አንቲ ውእቱ እመ ብርሃን
፫. ማርያም ወለደት ወልዳ ዘበኩራ
፬. አንተ ወአነ ሰማዕነ ቃለ እግዚአብሔር
፭. እለመኑ /እነማን/ ውእቶሙ ዘሖሩ ኀበ ገዳመ ሲና
ወደ ግእዝ መልስ /ወልጥ ኀበ ልሳነ ግእዝ/
፩. ወደ ጸሎት ቤት ሄድን።
፪. እኔ ነኝ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሄድኩ። /ዘ = የ/
፫. እነርሱ በኅብረት ተቀመጡ። /ኅቡረ = በኅብረት/
፬. ቶማስ እና ጴጥሮስ መምህራን ናቸው።
፭. ማርያም ድንግል የአሮን በትር /በትር = በትር/ ናት።
፮. አንተ የክርስቶስን ወንጌል ሰበክህ።
፯. አንተ ሰባኪ አይደለኽም።
፪.፩.፫. መራሕያን እንደ አመልካች ቅጽል
የመራሕያን ሌላው አገልግሎታቸው አንድን ነገር ወይም አካል በተባዕትና በአንስት፣ በማይታይና በሚታይ፣ በቅርብ ሩቅና በቅርብ ቅርብ አመልካች ጠቋሚ እየኾኑ መነገራቸው ነው። በሊቃዉንት መጻሕፍት ጉልት እየተባሉ ይጠቀሳሉ።
መደባቸዉም ሦስት ሲሆኑ እነዚኽም፦
፩. ተናጋሪን /እኔን ባይ/ አመልካቾች
፪. የማይታይ አመልካቾች
፫. የሚታይ አመልካቾች ናቸው። በተጨማሪ የቅርብ ሩቅ አመልካች ሆነው ሲገለጹ ደግሞ፦
ውእቱ ዝኩ ተብሎ ይገለጻል። ትርጉሙም ያ
ይእቲ እንትኩ >> >> ያቺ
ውእቶሙ እልኩ >> >> እኒያ /እነዚያ/
ውእቶን እልኮን >> >> እኒያ /ለሴቶች/
የሚከተሉትን ቃላት በማጥናት ከላይ ባየናቸው የመራሕያን አገልግሎት የራሳችሁን መልመጃዎች ሥሩ።
ሀ. ቃላት
ከመ = እንደ ወ = እና ጥቀ = እጅግ
አይቴ = ወዴት ማዕዜ = መቼ ናሁ = አሁን ፣ እነሆ
ምስለ = ጋር ምንት = ምን
እም = ከ በእንተ = ስለ
አላ = እንጂ ዝየ = እዚህ
ህየ = እዚያ ዮም = ዛሬ
ጌሠም = ነገ ትማልም = ትላንት
ዘ = እንተ = የ እለ ፣ ዘ = የ /ለብዙ/
(ዘሖረ = እንተ ሖረ =የሄደ) ምሳሌ: እለ ሖሩ = ዘሖሩ = የሄዱ
የቤተሰብእ ስም
ነጠላ ብዙ
አብ = አባት አበው = አባቶች
እም = እናት እማት = እናቶች
ወልድ = ልጅ /ወንድ/ ውሉድ = ልጆች
ወለት = ሴት ልጅ አዋልድ = ሴት ልጆች
እኅት = እኅት አኀት = እኅቶች
እኁ = ወንድም አኀው = ወንድሞች
አመት = ሴት አገልጋይ አእማት = ሴት አገልጋዮች
ገብር = ወንድ አገልጋይ አግብርት = ወንድ አገልጋዮች
ለ. የግስ ቃላት
ሖረ = ሄደ ፤ ቆመ = ቆመ ፤ ኖመ ፣ ደቀሰ = ተኛ
ጸለየ = ልመና አቀረበ ፤ ሰአለ = ለመነ ፣ ጠየቀ ፤ ነበረ = ተቀመጠ ፤ ኀደረ = አደረ
አርመመ = ዝም አለ ፤ ተፈስሐ = ተደሰተ ፤ ሰብሐ = አመሰገነ
በልዐ = በላ ፤ መጽአ = መጣ ፤ ቀተለ = ገደለ ሰትየ = ጠጣ
ምልማድ /መልመጃ/
የ “ሀ” ን ቃላት ከ “ለ” ቃላት ጋር /መራሕያኑን ከግሶች/ አዛምድ /አስተፃምር ቃላተ “ሀ” ምስለ ቃላተ “ለ”/
“ሀ” “ለ”
፩. አንትን አ. ነበርኩ
፪. ውእቱ በ. በላዕነ
፫. አነ ገ. ሖርኪ
፬. ውእቶን ደ. ቀተልክን
፭. ይእቲ ሀ. መጽአት
፮. ንሕነ ወ. ኖምክሙ
፯. አንቲ ዘ. ሖራ
፰. ውእቶሙ ሐ. በልዐ
፱. አንትሙ ጠ. ጸለዩ
ወልጥ ኀበ ልሳነ ዐምሐራ /ወደ አማርኛ ለውጥ/
፩. ንሕነ አብደርነ /አብደረ = መረጠ/ ንትገደፍ /ገደፈ = ተወ ፣ ጣለ/ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር እም ንንበር ውስተ ቤተ ኃጥአን።
፪. አንቲ ውእቱ መሶበ ወርቅ ንጹሕ
፫. አንተ ወአነ ሖርነ ኀበ መካነ ምስያጥ /ገበያ/
፬. ወለተ ማርያም ነጸረት መንገለ /ወደ/ ምስራቅ
፭. አንትሙ ሖርክሙ ኀበ ኢየሩሳሌም
፮. እለመኑ ውእቶሙ ዘነገዱ ኀበ ብሔረ እስራኤል
፯. ንሕነ ጸለይነ በእንተ ዴር ሡልጣን
፰. ውእቶሙ ተዐቀቡ እም ኤድስ
፱. አንትሙ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር
፲. አነ ደቀስኩ ላዕለ አራትየ
ወልጥ ኀበ ልሳነ ግእዝ
፩. አንተ አውሮጳዊ አይደለህም።
፪. የእናትህ ስሟ ማነው?
፫. ወንድሞች ወደ ቤተ ክርስቲያን መጡ።
፬. ሰሎሞን ወደ አባቶች ሄደ።
፭. ዝም ብሎ ተቀመጠ።
ትውውቅ /ሰላምታ/
ዜና ሥላሴ ቤዛ ማርያም
ሰላም ለከ እኁየ ወሰላም ለከ እኁየ
ሰላም ላንተ ይሁን ወንድሜ ሰላም ላንተም ይሁን
እፎ ሐሎከ እግዚአብሔር ይሰባሕ
እንዴት አለህ? እግዚአብሔር ይመስገን
መኑ ስምከ ቤዛ ማርያም ውእቱ ስምየ
ስምህ ማነው? ስሜ ቤዛ ማርያም ነው
ወመኑ ስመ አቡከ ዘድንግል ውእቱ ስመ አቡየ
የአባትህስ ስም ማነው? የአባቴ ስም ዘድንግል ነው
ወመኑ ስመ እምከ አስካለ ማርያም ውእቱ ስመ እምየ
እም አይቴ መጻእከ እም ጎጃም
ከየት ነው የመጣህ? ከጎጃም
እስፍንቱ አዝማኒከ ዕሥራ ወአሐዱ
ዕድሜህ ስንት ነው? ሃያ አንድ
ናሁ…ኀበ አይቴ ውእቱ ዘተሐውር ኀበ ከኒሳ
አሁን ወደ የት ነው የምትሄደው? ወደ ቤተ ክርስቲያን
እም አይቴ ውእቱ ዘትመጽእ ናሁ
እም መካነ ምሥያጥ አኹን ከየት ነው የምትመጣው?
ከገበያ ኦሆ = እሽ
ሰናይ ምስየት ለኲልነ
መልካም ምሽት ለኹላችን
No comments:
Post a Comment