ሰዋስወ ግእዝ
፪.፩. መራሕያን
መርሐ /መራ/ ከሚለው ግስ የተገኘ ሲሆን መሪዎች ፊታውራሪዎች የሚለውን ትርጉም ይይዛል። መራሕያን የሚባሉት በግእዝ ልሣን አስር ናቸው።
እነሱም ፦
አነ ………………………………እኔ
አንተ ……………………………አንተ
አንቲ ……………………………አንቺ
ውእቱ ……………………………እሱ
ይእቲ …………………………….እሷ
ንሕነ ……………………………..እኛ
አንትሙ ………………………….እናንተ /ለቅርብ ወንዶች/
አንትን ……………………………እናነተ /ለቅርብ ሴቶች/
ውእቶሙ /እሙንቱ/ …………….እነርሱ /ለሩቅ ወንዶች/
ውእቶን /እማንቱ/ …………………እነርሱ /ለሩቅ ሴቶች/
የመራሕያን አገልግሎት ሦስት ዓይነት ነው፡፡ ይኸዉም ፦
፩.፩. ተውላጠ ስም በመሆን
፩.፪. የመሆን ግስ /ነባር አንቀጽ/ በመሆንና
፩.፫. አመልካች ቅጽል በመሆን
፪.፩.፩. መራሕያን ምድብ ተውላጠ - ስሞች / pronouns /
መደብ ጾታ ነጠላ ቁጥር ብዙ ቁጥር
ሣልሳይ /ሦስተኛ መደብ/ ተባዕታይ ውእቱ ውእቶሙ /እሙንቱ/
አንስታይ ይእቲ ውእቶን /እማንቱ/
ካልኣይ /ኹለተኛ መደብ/ ተባዕታይ አንተ አንትሙ
አንስታይ አንቲ አንትን
ቀዳማይ /፩ኛ መደብ/ የወል አነ ንሕነ
በስም ፋንታ ተተክቶ የሚያገለግል ቃል ተውላጠ-ስም ይባላል። መራሕያን እንደ ተውላጠ-ስም ሲሆኑ በስም ፋንታ ተተክተው የሚነገሩ የርባታ መደቦች ናቸው። እነሱም የአካል፣ የስምና የስም አጸፋ እየሆኑ በወንድና በሴት፣ በሩቅና በቅርብ፣ በነጠላና በብዙ የሚነገረውን ርባታ ያሳያሉ። አስሩም መራሕያን በነጠላና በብዙ፣ በወንድና በሴት፣ በሩቅና በቅርብ ሲከፈሉ ሦስት መደብ ይሆናሉ።
ይኸዉም፦
፩. ቀዳማይ መደብ / 1st person/ አንደኛ መደብ፡ የወል ጾታ
አነ => እኔ = I
ንሕነ => እኛ = we
፪. ካልኣይ መደብ /2nd person/ ኹለተኛ መደብ፡
አንተ => በቁሙ = you
አንቲ => አንተ = you
አንትሙ => እናንተ = you (ለቅርብ ወንዶች)
አንትን => እናንተ = you (ለቅርብ ሴቶች)
፫. ሣልሳይ መደብ / 3rd person / ሦስተኛ መደብ፡
ውእቱ => እሱ = He
ይእቲ => እሷ = She
ውእቶሙ => እነሱ (እነዚያ) = They (ለሩቅ ወንዶች)
ውእቶን => እነሱ (እነዚያ) = They (ለሩቅ ሴቶች)
፩.፩. መራሕያን ምድብ ተውላጠ-ስሞች በዐረፍተ- ነገር
ተውላጠ-ስሞች ቀደሰ፣ ሖረ እና ሰገደ በሚሉት ቀዳማይ አንቀጾች ዐረፍተ- ነገር ሲመሠርቱ፦
ሀ. ቀደሰ / ቀዳማይ አንቀጽ፡ past tense/
አነ ቀደስኩ - እኔ አመሰገንሁ
አንተ ቀደስከ - አንተ አመሰገንህ
አንቲ ቀደስኪ - አንቺ አመሰገንሽ
ውእቱ ቀደሰ - እሱ አመሰገነ
ይእቲ ቀደሰት - እሷ አመሰገነች
ንሕነ ቀደስነ - እኛ አመሰገን
አንትሙ ቀደስክሙ - እናንተ አመሰገናችሁ
አንትን ቀደስክን - እናንተ አመሰገናችሁ (ለሴቶች)
ውእቶሙ ቀደሱ - እነሱ አመሰገኑ
ውእቶን ቀደሳ - እነሱ አመሰገኑ (ለሴቶች)
ማስታወሻ
• ውእቱ / ቀደሰ/ እና ይእቲ /ቀደሰት/ ከሚሉት ውጭ በሌሎች መራሕያን "ሰ" የሚለው ፊደል ወደ ሳድስ፣ ራብዕና ሳብዕ ይለወጣል፡፡
ለ. ሖረ = ሄደ /went/ ፣ ኀበ = ወደ
አነ ሖርኩ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - እኔ ወደ እግዚአብሔር ቤት ኼድኩ።
አንተ ሖርከ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - አንተ ወደ እግዚአብሔር ቤት ኼድክ።
አንቲ ሖርኪ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - You went to church (house of God).
ውእቱ ሖረ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - He went to church.
ይእቲ ሖረት ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ንሕነ ሖርነ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
አንትሙ ሖርክሙ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
አንትን ሖርክን ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ውእቶሙ ሖሩ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ውእቶን ሖራ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ሐ. ሰገደ = ሰገደ ፣ቅድመ = ፊት ለፊት
አነ ሰገድኩ ቅድመ ቤተ መቅደስ - በቤተ መቅደስ ፊት ሰገድሁ ።
አንተ ሰገድከ ቅድመ ቤተ መቅደስ - You fell on in front of church.
አንቲ ሰገድኪ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቱ ሰገደ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ይእቲ ሰገደት ቅድመ ቤተ መቅደስ
ንሕነ ሰገድነ ቅድመ ቤተ መቅደስ
አንትሙ ሰገድክሙ ቅድመ ቤተ መቅደስ
አንትን ሰገድክን ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቶሙ ሰገዱ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቶን ሰገዳ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ማስታወሻ
የግሱ መጨረሻ ፊደል ‹ከ› ፣‹ቀ› ፣‹ገ› ን የመሰለ ከሆነ ከዚያው ላይ ፊደሉን በማጥበቅ (አነ ፣አንተ ፣አንቲ፣ አንትሙ፣ አንትን ሲሆኑ) ይነበባል። ምሳሌ ሰበከ ብሎ አነ ሰበኩ ይባላል (ኩ ጠብቃ ትነበባለች) እንጅ አነ ሰበክኩ አይባልም። አነ አጥመቁ ይላል እንጅ አነ አጥመቅኩ አይልም። ስለሆነም ማጥበቅ አለብን።
፪.፩.፪. መራሕያን እንደ ነባር አንቀጽ / verb to be/
ነባር አንቀጽ ሲባል ማሰሪያ ግስ ማለት ነው። መራሕያን በአንቀጽነታቸው እየተተረጎሙ ሲፈቱ ማሠሪያ ይሆናሉ። ይኸዉም፦
ውእቱ = ነው፣ ኾነ፣ ነበረ፣ ኖረ፣ ይኑር፣ ነሽ፣ ነኝ፣ ነኽ፣ ናችሁ፣ ነበራችሁ
ይእቲ = ናት፣ ነበረች
ውእቶሙ(እሙንቱ) = ናቸው፣ ሆኑ፣ ነበሩ፣ ኖሩ፣ ይኑሩ ( ለወንዶች)
ውእቶን(እማንቱ) = ናቸው፣ ነበሩ (ለሴቶች)
አንተ = ነህ፣ ሆንክ፣ ነበርክ፣ ኖርክ፣ ኑር
አንቲ = ነሽ፣ ኾንሽ፣ ነበርሽ፣ ኖርሽ፣ ኑሪ
አንትሙ(ተባዕት) = ናችኹ፣ ኾናችኹ፣ ነበራችኹ፣ ኖራችኹ፣ ኑሩ
አንትን(አንስት) = ናችኹ፣ ኾናችኹ፣ ነበራችኹ፣ ኖራችኹ፣ ኑሩ
ንሕነ = ነን፣ ኾንን፣ ነበርን፣ ኖርን፣ እንኑር
አነ = ነኝ፣ ኾንኩ፣ ነበርኩ፣ ኖርኩ፣ ልኑር
ምሳሌ፦
አነ ውእቱ ጒንደ ወይን = እኔ የወይን ግንድ ነኝ።
አነ ውእቱ ኖላዊ ኄር = እኔ ቸር ጠባቂ ነኝ።
አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም= የአዳም /ለአዳም/ ተስፋው አንቺ ነሽ።
አንተ ውእቱ ዕጣን ኦ መድኃኒነ = መድኃኒታችን ሆይ አንተ ዕጣን ነህ።
ማርያም ይእቲ መሠረተ ሕይወት = ማርያም የሕይወታችን መሠረት ናት።
ናሆም ወሚልክያስ ነቢያት ውእቶሙ /እሙንቱ/ = ናሆምና ሚልክያስ ነቢያት ናቸው።
አስቴር ወሶስና ቅዱሳን ውእቶን /እማንቱ/ = አስቴርና ሶስና ቅዱሳን ናቸው።
ውእቱ ለዋጭ ተለዋጭ ባሕርይ ስላለው በተባዕትና በአንስት በብዙና በነጠላ አፈታት ይፈታል። እንዲህ ማለት በነባር አንቀጽነቱ የሚከተሉትን ትርጉም ሊያስገኝ ይችላል። በዐረፍተ- ነገር እየገባ ሲታይ የትኛውን ትርጉም እንደያዘ ዐመሉን ማስተዋል ያስፈልጋል።
ውእቱ = ነው፣ ናት፣ ናቸው /ተ/አ/፤
= ነኽ፣ ነሽ፣ ናችኹ /ተ/አ/ ፤
= ነኝ፣ ነን፣ ይኾናል
ሥርዓተ ዐረፍተ- ነገር በምሳሌ፦
• ቅድስት ይእቲ ኤልሳቤጥ = ኤልሳቤጥ ቅድስት ናት
• ኤልሳቤጥ ቅድስት ይእቲ
• ነቢይ ውእቱ ሕዝቅኤል
• ሕዝቅኤል ነቢይ ውእቱ
ውእቱ ለሚለው አሉታው አኮ /አይደለም/ ነው
ለምሳሌ፦ አኮ ነቢይ ሕዝቅኤል
ተጨማሪ ምሳሌዎች:
አነ ውእቱ ፍኖተ ጽድቅ = እኔ የእውነት መንገድ ነኝ
አንተ ውእቱ ቤዛ ኵሉ ዓለም = አንተ የዓለም ሁሉ ቤዛ ነህ
ጳዉሎስ ወጴጥሮስ መምህራን ውእቶሙ
ሰሎሜ ወኤልሳቤጥ ቅዱሳት ውእቶን
አበዊነ መሀሩነ ልሳነክሙ ወቃለ እግዚአብሔር
መርሐ /መራ/ ከሚለው ግስ የተገኘ ሲሆን መሪዎች ፊታውራሪዎች የሚለውን ትርጉም ይይዛል። መራሕያን የሚባሉት በግእዝ ልሣን አስር ናቸው።
እነሱም ፦
አነ ………………………………እኔ
አንተ ……………………………አንተ
አንቲ ……………………………አንቺ
ውእቱ ……………………………እሱ
ይእቲ …………………………….እሷ
ንሕነ ……………………………..እኛ
አንትሙ ………………………….እናንተ /ለቅርብ ወንዶች/
አንትን ……………………………እናነተ /ለቅርብ ሴቶች/
ውእቶሙ /እሙንቱ/ …………….እነርሱ /ለሩቅ ወንዶች/
ውእቶን /እማንቱ/ …………………እነርሱ /ለሩቅ ሴቶች/
የመራሕያን አገልግሎት ሦስት ዓይነት ነው፡፡ ይኸዉም ፦
፩.፩. ተውላጠ ስም በመሆን
፩.፪. የመሆን ግስ /ነባር አንቀጽ/ በመሆንና
፩.፫. አመልካች ቅጽል በመሆን
፪.፩.፩. መራሕያን ምድብ ተውላጠ - ስሞች / pronouns /
መደብ ጾታ ነጠላ ቁጥር ብዙ ቁጥር
ሣልሳይ /ሦስተኛ መደብ/ ተባዕታይ ውእቱ ውእቶሙ /እሙንቱ/
አንስታይ ይእቲ ውእቶን /እማንቱ/
ካልኣይ /ኹለተኛ መደብ/ ተባዕታይ አንተ አንትሙ
አንስታይ አንቲ አንትን
ቀዳማይ /፩ኛ መደብ/ የወል አነ ንሕነ
በስም ፋንታ ተተክቶ የሚያገለግል ቃል ተውላጠ-ስም ይባላል። መራሕያን እንደ ተውላጠ-ስም ሲሆኑ በስም ፋንታ ተተክተው የሚነገሩ የርባታ መደቦች ናቸው። እነሱም የአካል፣ የስምና የስም አጸፋ እየሆኑ በወንድና በሴት፣ በሩቅና በቅርብ፣ በነጠላና በብዙ የሚነገረውን ርባታ ያሳያሉ። አስሩም መራሕያን በነጠላና በብዙ፣ በወንድና በሴት፣ በሩቅና በቅርብ ሲከፈሉ ሦስት መደብ ይሆናሉ።
ይኸዉም፦
፩. ቀዳማይ መደብ / 1st person/ አንደኛ መደብ፡ የወል ጾታ
አነ => እኔ = I
ንሕነ => እኛ = we
፪. ካልኣይ መደብ /2nd person/ ኹለተኛ መደብ፡
አንተ => በቁሙ = you
አንቲ => አንተ = you
አንትሙ => እናንተ = you (ለቅርብ ወንዶች)
አንትን => እናንተ = you (ለቅርብ ሴቶች)
፫. ሣልሳይ መደብ / 3rd person / ሦስተኛ መደብ፡
ውእቱ => እሱ = He
ይእቲ => እሷ = She
ውእቶሙ => እነሱ (እነዚያ) = They (ለሩቅ ወንዶች)
ውእቶን => እነሱ (እነዚያ) = They (ለሩቅ ሴቶች)
፩.፩. መራሕያን ምድብ ተውላጠ-ስሞች በዐረፍተ- ነገር
ተውላጠ-ስሞች ቀደሰ፣ ሖረ እና ሰገደ በሚሉት ቀዳማይ አንቀጾች ዐረፍተ- ነገር ሲመሠርቱ፦
ሀ. ቀደሰ / ቀዳማይ አንቀጽ፡ past tense/
አነ ቀደስኩ - እኔ አመሰገንሁ
አንተ ቀደስከ - አንተ አመሰገንህ
አንቲ ቀደስኪ - አንቺ አመሰገንሽ
ውእቱ ቀደሰ - እሱ አመሰገነ
ይእቲ ቀደሰት - እሷ አመሰገነች
ንሕነ ቀደስነ - እኛ አመሰገን
አንትሙ ቀደስክሙ - እናንተ አመሰገናችሁ
አንትን ቀደስክን - እናንተ አመሰገናችሁ (ለሴቶች)
ውእቶሙ ቀደሱ - እነሱ አመሰገኑ
ውእቶን ቀደሳ - እነሱ አመሰገኑ (ለሴቶች)
ማስታወሻ
• ውእቱ / ቀደሰ/ እና ይእቲ /ቀደሰት/ ከሚሉት ውጭ በሌሎች መራሕያን "ሰ" የሚለው ፊደል ወደ ሳድስ፣ ራብዕና ሳብዕ ይለወጣል፡፡
ለ. ሖረ = ሄደ /went/ ፣ ኀበ = ወደ
አነ ሖርኩ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - እኔ ወደ እግዚአብሔር ቤት ኼድኩ።
አንተ ሖርከ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - አንተ ወደ እግዚአብሔር ቤት ኼድክ።
አንቲ ሖርኪ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - You went to church (house of God).
ውእቱ ሖረ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር - He went to church.
ይእቲ ሖረት ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ንሕነ ሖርነ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
አንትሙ ሖርክሙ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
አንትን ሖርክን ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ውእቶሙ ሖሩ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ውእቶን ሖራ ኀበ ቤተ እግዚአብሔር
ሐ. ሰገደ = ሰገደ ፣ቅድመ = ፊት ለፊት
አነ ሰገድኩ ቅድመ ቤተ መቅደስ - በቤተ መቅደስ ፊት ሰገድሁ ።
አንተ ሰገድከ ቅድመ ቤተ መቅደስ - You fell on in front of church.
አንቲ ሰገድኪ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቱ ሰገደ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ይእቲ ሰገደት ቅድመ ቤተ መቅደስ
ንሕነ ሰገድነ ቅድመ ቤተ መቅደስ
አንትሙ ሰገድክሙ ቅድመ ቤተ መቅደስ
አንትን ሰገድክን ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቶሙ ሰገዱ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ውእቶን ሰገዳ ቅድመ ቤተ መቅደስ
ማስታወሻ
የግሱ መጨረሻ ፊደል ‹ከ› ፣‹ቀ› ፣‹ገ› ን የመሰለ ከሆነ ከዚያው ላይ ፊደሉን በማጥበቅ (አነ ፣አንተ ፣አንቲ፣ አንትሙ፣ አንትን ሲሆኑ) ይነበባል። ምሳሌ ሰበከ ብሎ አነ ሰበኩ ይባላል (ኩ ጠብቃ ትነበባለች) እንጅ አነ ሰበክኩ አይባልም። አነ አጥመቁ ይላል እንጅ አነ አጥመቅኩ አይልም። ስለሆነም ማጥበቅ አለብን።
፪.፩.፪. መራሕያን እንደ ነባር አንቀጽ / verb to be/
ነባር አንቀጽ ሲባል ማሰሪያ ግስ ማለት ነው። መራሕያን በአንቀጽነታቸው እየተተረጎሙ ሲፈቱ ማሠሪያ ይሆናሉ። ይኸዉም፦
ውእቱ = ነው፣ ኾነ፣ ነበረ፣ ኖረ፣ ይኑር፣ ነሽ፣ ነኝ፣ ነኽ፣ ናችሁ፣ ነበራችሁ
ይእቲ = ናት፣ ነበረች
ውእቶሙ(እሙንቱ) = ናቸው፣ ሆኑ፣ ነበሩ፣ ኖሩ፣ ይኑሩ ( ለወንዶች)
ውእቶን(እማንቱ) = ናቸው፣ ነበሩ (ለሴቶች)
አንተ = ነህ፣ ሆንክ፣ ነበርክ፣ ኖርክ፣ ኑር
አንቲ = ነሽ፣ ኾንሽ፣ ነበርሽ፣ ኖርሽ፣ ኑሪ
አንትሙ(ተባዕት) = ናችኹ፣ ኾናችኹ፣ ነበራችኹ፣ ኖራችኹ፣ ኑሩ
አንትን(አንስት) = ናችኹ፣ ኾናችኹ፣ ነበራችኹ፣ ኖራችኹ፣ ኑሩ
ንሕነ = ነን፣ ኾንን፣ ነበርን፣ ኖርን፣ እንኑር
አነ = ነኝ፣ ኾንኩ፣ ነበርኩ፣ ኖርኩ፣ ልኑር
ምሳሌ፦
አነ ውእቱ ጒንደ ወይን = እኔ የወይን ግንድ ነኝ።
አነ ውእቱ ኖላዊ ኄር = እኔ ቸር ጠባቂ ነኝ።
አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም= የአዳም /ለአዳም/ ተስፋው አንቺ ነሽ።
አንተ ውእቱ ዕጣን ኦ መድኃኒነ = መድኃኒታችን ሆይ አንተ ዕጣን ነህ።
ማርያም ይእቲ መሠረተ ሕይወት = ማርያም የሕይወታችን መሠረት ናት።
ናሆም ወሚልክያስ ነቢያት ውእቶሙ /እሙንቱ/ = ናሆምና ሚልክያስ ነቢያት ናቸው።
አስቴር ወሶስና ቅዱሳን ውእቶን /እማንቱ/ = አስቴርና ሶስና ቅዱሳን ናቸው።
ውእቱ ለዋጭ ተለዋጭ ባሕርይ ስላለው በተባዕትና በአንስት በብዙና በነጠላ አፈታት ይፈታል። እንዲህ ማለት በነባር አንቀጽነቱ የሚከተሉትን ትርጉም ሊያስገኝ ይችላል። በዐረፍተ- ነገር እየገባ ሲታይ የትኛውን ትርጉም እንደያዘ ዐመሉን ማስተዋል ያስፈልጋል።
ውእቱ = ነው፣ ናት፣ ናቸው /ተ/አ/፤
= ነኽ፣ ነሽ፣ ናችኹ /ተ/አ/ ፤
= ነኝ፣ ነን፣ ይኾናል
ሥርዓተ ዐረፍተ- ነገር በምሳሌ፦
• ቅድስት ይእቲ ኤልሳቤጥ = ኤልሳቤጥ ቅድስት ናት
• ኤልሳቤጥ ቅድስት ይእቲ
• ነቢይ ውእቱ ሕዝቅኤል
• ሕዝቅኤል ነቢይ ውእቱ
ውእቱ ለሚለው አሉታው አኮ /አይደለም/ ነው
ለምሳሌ፦ አኮ ነቢይ ሕዝቅኤል
ተጨማሪ ምሳሌዎች:
አነ ውእቱ ፍኖተ ጽድቅ = እኔ የእውነት መንገድ ነኝ
አንተ ውእቱ ቤዛ ኵሉ ዓለም = አንተ የዓለም ሁሉ ቤዛ ነህ
ጳዉሎስ ወጴጥሮስ መምህራን ውእቶሙ
ሰሎሜ ወኤልሳቤጥ ቅዱሳት ውእቶን
አበዊነ መሀሩነ ልሳነክሙ ወቃለ እግዚአብሔር
Sega Genesis Classic Game Console Flashback Review - Top
ReplyDeleteIf you enjoy the same original Sega Genesis games, then you should 카지노사이트 also try the Astro 바카라사이트 City Portable Mega Drive Flashback Gaming Console Flashback